ከበደ ሚካኤል በኢትዮጵያ ሥነፅሁፍ ታሪክ ውስጥ ገናና ከሆኑት ደራስያን አንዱ ናቸው። ጥቅምት 23፣ 1909 የተወለዱት ባለ ቅኔ የቤተክህነትን ትምህርት ካገባደዱ በኋላ በአሊያንስ ፍራንሴዝና በላዛሪስት ሚስዮን ዘመናዊ ትምህርትን ተከታትለዋል። የግሪክ፣ የሮማውያን፣ የእንግሊዝ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርመን፣ የሩስያና የጣሊያንን በርካት መፃህፍት ከመረመሩም በኋላ ሃያ ስድስት መፃህፍትን ለወገኖቻቸው አበርክተዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለዚሁ አስተዋፅኦዋቸው የክብር ዶክተርነት ዲርሪን በ1990 በሰጠበት ወቅትም፣ <<በድርሰቶቻቸው ውስጥ የሚታዩት የእኒህ ታላቅ ደራሲ የሃሳብ መግለጫዎች፣ ቃላት፣ ዘይቤዎች፣ ሌሎች የአፃፃፍ ስልት ገፅታዎች በኋላ ለመጡ ደራሲዎች ያደረጉት አስተዋፅኦ ቀላል አይደለም። በተለይ ከ1950ዎቹ ወዲህ የተነሱ በርካታ ደራሲዎች የሳቸውን ድርሰቶች አንብበው፣ በሳቸው ድርሰቶች ሥነፅሁፍን አውቀውና አጣጥመው ደራሲ ሊሆኑ በቅተዋል>> ብሏል።ሜጋ አሳታሚ ድርጅትም የኒህን ሊቅ ሥራዎች ጠቃሚነት በማጤንና ለዘመናችን ትውልድ የሚኖራቸውን ፋይዳም በማሰብ የሚከተሉትን መፅሐፎቻቸውን ለአንባብያን አቅርቧል።1᎐ ታሪክና ምሣሌ (፩ኛ መፅሐፍ)2᎐ ታሪክና ምሣሌ (፪ኛ መፅሐፍ)3᎐ የቅኔ ውበት4᎐ ሮሜዎና ዡልየት5᎐ የዕውቀት ብልጭታ6᎐ ጃፓን እንደምን ሠለጠናች?7᎐ ታላላው ሰዎች