ይሉኝታ yelugneta.com

የራሴ ዝርዝሮችወደ የራሶ ሥፍራ

የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847 እስከ 1983

ባሕሩ ዘውዴ

ወደቋት
ዋጋ 110 ብር
facebook
በመጀመሪያ በእንግሊዘኛ በታተመበት ጊዜ ዕውቅ ምሁራን የሰጡት አስተያየት፤
ለረጅም ጊዜ የኢትዮጵያ ታሪክ መጽሐፍ እጦት አሁን በሚያስደስት ሁኔታ ተሟልቷል። እንዲህ ያለን መጽሐፍ መጻፍ በብዙ መንገድ አዳጋች ቢሆንም፤ ደራሲው ግዴታውን በሚገባ ተወጥቶታል። የነገሥታትና የጦረኞችን የፓለቲካ ታሪክ ብቻ ሳይሆን ኤኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ክንዋኔዎችን ያትታል። ያገር ውስጥ ክስተቶች ከውጭ እያደገ ከሚመጣው ግፊት ጋር ተዛምደዋል። የደራሲው አስተያየቶች ውል ያልሳቱና ብርሃን የሚፈነጥቁ ናቸው። በውስጡ ያሉት አያሌ ፎቶግራፎች ለመጽሐፉ ተጨማሪ ዋጋ ሰጥተውታል።
ፕሮፌሰር ክርስቶፈር ካላፕሃም
ላንካስተር ዩኒቨርሲቲ
(እንግሊዝ)

ከአፄ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግሥት መጀመሪያ አንስቶ እስከ 1966 አብዮት ላለው የኢትዮጵያ ታሪክ ከዚህ የተሻለ መጽሐፍ አለ ብሎ ማሰብ ያዳግታል። መጽሐፉ ብዙ መረጃዎችን ይዞ አዳዲስ ግኝቶችንም ይፈነጥቃል። በኢትዮጵያዊ ደራሲ የተጻፈ የመጀመሪያው የቅርብ ዘመን የኢትዮጵያ ታሪክ በመሆኑም ልዩ ግምት ይሰጠዋል።
ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት
የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም
(አዲስ አበባ)

ስለ ሁለተኛው የእንግሊዝኛ እትም የተሰጠ አስተያየት
ሁለተኛው እትም ውስጥ የተካተተው አዲስ ምዕራፍ (ምዕራፍ 6) የዘመናዊቱ ኢትዮጵያን ታሪክ ለመረዳት ለሚሻ አንባቢ ሁሉ መጽሐፉ ያለውን ዋጋ ይበልጥ ያጎላዋል። በ44 ገጾች ተጨምቆ የቀረበው የአብዮቱ ዘመን ታሪክ በ1970ዎቹ የተፃፉትን አያሌ መጻሕፍት፥ የድኅረ ምረቃ ተማሪዎችን ጥናትና የደራሲውንም የየግል ተሞክሮ አጣቅሶ በጥንቃቄ የተቀመመ በመሆኑ፤ ራሱን የቻለ ዋጋ ያለው ነው። እንደ መጀመሪያው እትም ሁሉ፤ ትረካው ብርቅ በሆኑ ፎቶግራፎች የተቀነባበረ ነው። ባጭሩ ተሻሽሎና ዳብሮ የቀረበ ትልቅ ዋጋ ያለው መጽሐፍ ነው።

የመመዝግቢያ ቅጽ

ስም
የአባት ስም
የአያት ስም
የመጠቀሚያ ስም
የመጠቀሚያ የሚስጢር ቃል
የሚስጢር ቃል እንደገና ፃፍ
ለመግዛት ለመሸጥ ለሁለቱም

ወደ የራሶ ሥፍራ ለመግባት

የመጠቀሚያ ስም
የመጠቀሚያ የሚስጢር ቃል

ወደ የራሶ ሥፍራ ለመግባት

የመጠቀሚያ ስም
የመጠቀሚያ የሚስጢር ቃል

የመላኪያ አስራሻዎን ያስገቡ

ሁሉም መልዕክቶች በEMS (ኢኤምኤስ) ስለሚላኩ አድራሳዎን ስም እስከ አያት ፡ ስልክ ቁጥር (መድረሱን ደውለው የሚያረጋግጡበት ስለሆነ) ፡ የቤት ቁጥር ፡ የአካባቢ ስም(የጎጥ ስም) ፡ የቀበሌ ስም ፡ ወረዳ ፡ ክልል በማለት ያስገቡ።


X